Author: Author

“ተንኳሾቹ” መጽሐፍ ለንባብ በቃ ነዋሪነቱን በደቡብ ኮሪያ ያደረገው ጋዜጠኛ ዳዊት ንጉሡ ረታ (ዳ ን ረ) ለራሱ ሁለተኛ የሆነው መፅሃፉን ” ተንኳሾቹ ” በሚል ርዕስ ለህትመት አብቅቷል። “ተንኳሾቹ ” መፅሃፍ 310 ገፆች ያሉትና ሃያ አንጋፋና ወጣት አዋቂዎችንና ታዋቂዎችን በእንግድነት ጋብዞ ለአንባቢያን ኮርኳሪ ሃሳቦቻቸውን እንዲያካፍሉ ያስቻለበት መፅሃፉ እንደሆነ ዳዊት ንጉሡ ለዝግጅት ክፍላችን ተናግሯል። ከዚህ ቀደም “በ97 እና ሌሎች ታሪኮች” በሚል የመጀመሪያ መፅሃፉን ያቀረበልን ዳዊት ሁለተኛ መፅሃፉ ተንኳሾቹን በአገር ውስጥ በብር አራት መቶ ሃምሳ ብቻ ለአንባቢያን እንዳቀረበ ገልፆልናል። መጽሃፉ የመጀመሪያ ዙር ውስን ቁጥር ህትመቱ በደቡብ ኮሪያ የተከናወነ ሲሆን ለአገር ቤት አንባቢያን ደግሞ በአገር ውስጥ ለማሳተም ከአሳታሚዎችና አከፋፋዮች ጋር ውይይት በማድረግ ሂደት ላይ እንዳለም…

Read More

የሳምንቱን ኪናዊ መረጃዎችን እነሆ: 📍መረጃውን ሲጠቀሙ ምንጭ ይጠቀሱ 1.አንጋፋዋ ድምጻዊት ሐመልማል አባተ “ራያ” የተሰኘ ነጠላ ሙዚቃዋን በቅርቡ ለአድማጮች እንደምታደርስ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል። የሙዚቃው ግጥምና ዜማ  በቢኒያም ረዳኢ (ሀ ግዕዝ ) ተሰርቷል። በሙዚቃ ቅንብር፣ ሚክሲንግና ማስተሪንጉ ላይ አሌክስ ይለፍ ተሳትፏል። 2.የድምጻዊ አቡሽ ዘለቀ ” ሀገር እና ሰው” የተሰኘ የሙዚቃ ስራ ነገ አርብ ሐምሌ 5 2016 ዓ.ም ዩቲዩብን ጨምሮ በተለያዩ ዓለምአቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች ላይ ለአድማጮች ይደርሳል። የሙዚቃው ግጥምና ዜማ የአቡሽ ዘለቀ ሲሆን ሙዚቃ ቅንብሩ ደግሞ ቤካ ነው። 3.”ኦሎምፒክ ኮንሰርት” ተራዘመ። በዚህ ሳምንት ሐምሌ 6 2016 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ ሊካሄድ ታስቦ የነበረው “ኦሎምፒክ ኮንሰርት ” ለሐምሌ 13 2016 ዓ.ም እንደተራዘመ ኤቨንት አዲስ…

Read More

የሳምንቱ ኪናዊ መረጃዎች ቀጥሎው ይቀርባሉ! መረጃውን ሲጠቀሙ ምንጭ ይጠቀሱ! 📍የአንጋፋው ጋዜጠኛ ፣ገጣሚ፣ ደራሲና ተርጓሚ ነቢይ መኮንን የሽኝትና ቀብር ሥነሥርዓት ዛሬ ሰኔ 27 2016 ዓ.ም ይፈፀማል።የሽኝት መርሐግብሩ ከጠዋቱ 3:30 እስከ 5:00 በብሔራዊ ቴአትር የሚካሄድ ሲሆን ከቀኑ 9:00 ላይ በአዳማ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የቀብር ሥነሥርዓቱ ይፈፀማል ተብሏል። 📍ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ በ”USA TOUR” በአሜሪካ ከዛሬ ጀምሮ የሙዚቃ ስራውን ማቅረብ ይጀምራል ተብሏል። ሙዚቀኛው ዛሬ በአትላንታ የሙዚቃ ስራውን ማቅረብ የሚጀምር ሲሆን በማስከተል በስድስት የአሜሪካ ግዛቶች የሙዚቃ ኮንሰርቱን እንደሚያቀርብ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል። ይህም የሙዚቃ ዝግጅት ጉዞው የሮፍናን ኑሪ ዘጠኛ(ኖር እና ሐራንቤ) አልበም ከተለቀቀ በኃላ የመጀመሪያው ነው። 📍የድምጻዊት ሰላማዊት ዮሐንስ “ሰንቢደ” የተሰኘ የትግርኛ ሙዚቃ ነገ በናሆም…

Read More

ታላቁ የጥበብ ሰው ነቢይ መኮንን ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 26 2016 ዓ.ም ማረፉ ተሰምቷል።ስለዚህ ግዙፍ ኢትዮጵያዊ የጥበብ ሰው ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ያገኘውን መረጃ እንደሚከተለው ያቀርባል። 📍ነበይ መኮንን አንጋፋ ጋዜጠኛ፣ ደራሲ ፣ ገጣሚ እና ትርጓሜ ነው። 📍ጋዜጠኛው ነቢይ መኮንን -አንጋፋው ጋዜጠኛ ነቢይ መኮንን ለረጅም ዓመታት የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሰርቷል። -ነቢይ መኮንን ከአዲስ አድማስ መሥራቾች አንዱ ሲሆን በዋና አዘጋጅነት ጋዜጣዋን በመምራት ተወዳጅ ካደረጓት በቀዳሚነት ስሙ ይጠቀሳል። 📍ገጣሚው ነቢይ መኮንን ገጣሚ ነቢይ መኮንን፤ “ስውር ስፌት” ቁጥር አንድና ሁለት፣ የግጥም መድበሎችን ጨምሮ በርካታ የግጥም ስራዎችን በተለያዩ መድረኮች በማቅረብ ይታወቃል፡፡ 📍ደራሲው ነቢይ መኮንን “የኛ ሰው በአሜሪካ” እና “የመጨረሻው ንግግር ” የተሰኙ መጻሕፍቱ ዝነኛ ስራዎቹ…

Read More

አርቲስት ትዕግሥት ግርማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማህበር የበጎ ፍቃድ አምባሳደር ሆና ተሾመች አለምአቀፋዊ ማህበር የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማህበር አርቲስት ትዕግሥት ግርማን የበጎ ፍቃድ አምባሳደር አድርጎ እንደሾመ ዛሬ ሰኔ 20 2016 ዓ.ም በቤስት ዌስተርን ፕላስ ሆቴል በተካሄደ የፊርማ ሥነሥርዓት ወቅት ገልጿል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሕክምና ማህበር ምስረታውን ካደረገበት ጊዜ እንስቶ ዘር፣ ቀለም ሀይማኖትም ሆነ ማንነት ያልገደበው ሰብዓዊ ድጋፍ እና አገልግሎትን በኢትዮጵያ የተለያዩ አከባቢዎች እየተዘዋወር በመስጠት ላይ የሚገኝ ማህበር ነው ተብሏል። ማህበሩ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች 35 የሚሆኑ የህክምና ጉዞዎችን በማድረግ ሰብዓዊነትን ባስቀደመ ተግባሩ ከ25 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሰብዓዊ…

Read More

የሳምንቱ ኪናዊ መረጃዎች ቀጥሎው ይቀርባሉ! 📍የድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሣሁን(ቴዲ አፍሮ) የሙዚቃ ኮንሰርት የፊታችን እሁድ ሰኔ 23 2016 ዓ.ም 17 ሺ ተመልካቾችን በሚያስተናግደው የሙዚቃ እና ሌሎች የመዝናኛ ዘርፎች ማቅረቢያ በሆነው በዱባዩ ኮካኮላ አሬና ስታዲየም ውስጥ ይካሄዳል። ድምጻዊው ለዚህ የሙዚቃ ዝግጅቱ ከቀናት በፊት ዱባይ መግባቱ ይታወሳል። 📍የድምጻዊ አብዱ ኪያር “ፓፓፓ” የተሰኘ አልበም ነገ ሰኔ 21 2016 ዓ.ም በራሱ ዩቲዩብ ቻናል እና በዓለምአቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች ላይ ይለቀቃል። በአልበሙ ላይ በቅንብር ስማገኘሁ ሳሙኤል፣ ኪሩቤል ተስፋዬ፣ ካሙዙ ካሳ እና ዳዊት ቦስኮ ተሳትፈዋል። ሚክሲንጉን የሰሩት ስማገኘሁ ሳሙኤል እና ኪሩቤል ተስፋዬ ሲሆኑ ማስተሪንግ ደግሞ በአበጋዝ ክብረወርቅ ተሰርቷል። 📍የድምጻዊት ለምለም ኃ/ሚካኤል “ማያዬ” የአልበም ምርቃት የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 22 2016…

Read More

የሳምንቱ ኪናዊ መረጃዎች ቀጥሎ ይቀርባሉ! መረጃውን ሲጠቀሙ ምንጭ ይጠቅሱ! 📍ሙዚቃ የድምፃዊ ጉቱ አበራ “ጋፊኮ” የተሰኘ የመጀመሪያ አልበም ነገ አርብ ሰኔ 14 2016 ዓ.ም የድምጻዊው ዩቲዩብ ቻናልን ጨምሮ በተለያዩ ዓለምአቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች ላይ ይለቀቃል ተብሏል። “ጋፊኮ” አልበም ስምንት የሙዚቃ ስራዎችን ይዟል። ጉቱ አበራ ከዚህ ቀደም ሀዋንሀዋ፣ ዴሚ፣ አነቱ፣ኢዮሌ የተሰኙ ሙዚቃዎችን ለአድማጮች ማድረሱ አይዘነጋም። የድምፃዊ ወንደሰን መኮንን በመድረክ ስሙ (ወንዲ ማክ) “ይንጋልሽ” የተሰኘ አዲስ አልበም ነገ አርብ ሰኔ 14 2016 ዓ.ም ለአድማጮች እንደሚደርስ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል።14 ሙዚቃዎችን የያዘው አልበሙ ግጥም እና ዜማው በራሱ በወንዲ ማክ ተሰርቷል። በፍቅር፣ በማህበራዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥን እንደሆነ ተነግሯል።ይህም አልበም ዩቲዩብን ጨምሮ በተለያዩ ዓለምአቀፍ የሙዚቃ…

Read More

የሳምንቱ ኪናዊ መረጃዎች ቀጥሎ ይቀርባሉ! ሚዲያዎች መረጃውን ስትጠቀሙ ምንጭ ጥቀሱ❗️ 📍መጽሐፍ የገጣሚ ኤፍሬም ስዩም አንድ መጽሐፍ በአንድ ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ለህትመት ሊበቃ እንደሆነ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል። “ቡና እና ምልኪ” የተሰኘውና ከዓመት በፊት ለንባብ ይበቃል ተብሎ የዘገየው መጽሐፍ ከፊታችን ቅዳሜ ጀምሮ በማህበራዊ ትስስር ገፅ በሚደረግ ቅድም ክፍያ እንደሚታተም ገጣሚው አስታውቋል። ገጣሚው በማህበራዊ ትስስር ገፁ”በሀርድ ኮፒ ያጌጠ ምልኪና ቡና ከቅዳሜ ጀምሮ 1000 ኮፒ ህትመት በ1000 ብር ብቻ እጃችሁና የመጻሕፍት ሼልፋችሁ ላይ ለማኖር ዝግጅት አድርጉ” ብሏል። የገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ አዲስ መጽሐፍ ለንባብ በቃ። መጽሐፉ “የጊዜ ሠሌዳ” የተሰኘ ርዕስ የተሰጠው የግጥም ስብስብ መጽሐፍ ነው።በ103 ገፆች ተቀንብቡ በ250 የጀርባ ዋጋ ለአንባቢያን የቀረበ ሲሆን…

Read More

የግጥምና ዜማ ደራሲ አለማየሁ ደመቀ የ25 ዓመት የሙዚቃ ጉዞ የሚዘከርበት ኮንሰርት ቅዳሜ ይካሄዳል የተወዳጁ የሙዚቃ ግጥምና ዜማ ደራሲውን አለማየሁ ደመቀን የሩብ ክ/ዘመናት የሙዚቃ ጉዞ የሚያወሳ እና እርሱንም የሚዘክር “ዮቶር ድግስ” የተሰኘ የሙዚቃ ኮንሰርት የፊታችን ቅዳሜ ሰኔ 15 2016 ዓ.ም በማሪዮት ሌግዥሪ ሆቴል ይካሄዳል ተብሏል። በሙዚቃ ባለሙያው የ25 ዓመታት ጉዞ ውስጥ የእርሱን ተወዳጅ እና ዘመን ተሻጋሪ የግጥምና ዜማ ስራዎች ወስደው ከተጫወቱ ድምፃውያን መካከል ጎሳዬ ተስፋዬ ፣ኃይልዬ ታደሰ ፣ አብነት አጎናፍር ፣ግርማ ተፈራ ካሣ ፣ ሐሊማ አብዱራህማን፣ ሔለን በርሔ ፣ ዳዊት ፅጌ ፣ብስራት ሱራፌል ፣ አዲስ ለገሰ፣አንተነት ምናሉ ፣ አበባው ጌታቸው ፣ ዳግማዊ ታምራት ፣መስከረም ኡስማን በኮንሰርቱ ላይ እንደሚሳተፉ የሙዚቃ ስራቸውንም እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።…

Read More

“ምን ሆኛለሁ?” መጽሐፍ በቅርቡ ለንባብ ይበቃል የሥነልቦና ባለሞያዋ ትዕግስት ዋልተንጉስ እና ጋዜጠኛና ደራሲ ቴዎድሮስ ተክለአረጋይ የተጣመሩበት ‘ምን ሆኛለሁ?’ መፅሀፍ በጣም በቅርቡ ታትሞ ይወጣል ተብሏል። “የምታደርጉት ድርጊት ግራ አጋብቷችሁ ‘ምን ሆኛለሁ?’ ብላችሁ ከጠየቃችሁ ይሄ መፅሀፍ ልጅነታችሁን በመመርመር ራሳችሁን በተሻለ እንድትረዱ ያግዛችኋል”። በተጨማሪም “በዙሪያችሁ ያሉ ሰዎች ወይም በቲቪ የምታውቋቸው ነጋዴዎች፣ ፖለቲከኞች፣ ታዋቂ ሰዎች የሚያደርጉት ድርጊት አልገባ ብሏችሁ ‘ምን ሆኖ ነው?’ ወይም ‘ምን ሆና ነው?’ የሚል ጥያቄ ከፈጠረባችሁ ይሄ መፅሀፍ ጥሩ የፅንሰ ሀሳብ መነፅር ይሰጣችኋል ” ስለመባሉ ኤቨንት አዲስ ድረገፅ ሰምቷል። “ምን ሆኛለሁ” የተሰኘውን መጽሐፍ ብዙዎች መፅሀፉን ቀድመው እየገዙ እንደሆነም ተመልክተናል። ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1

Read More